የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ እና የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መንገድ ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች የታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ አስመልክቶ በክልል ደረጃ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ተሳትፈዋል።

 በድጋፍ ሰልፉም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዳግም አድዋ ድል እና የህልውናችን መሰረት ስለመሆኑ፥ ስንተባበር የምንችል መሆኑን የሚገልፁና ሌሎች መፈክሮችን በማሰማት ሰራተኞች በከፍተኛ ስሜት የድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊ ሆነዋል።