‹‹የአማራ ገጠር መንገዶች ድርጅት›› በሚል ስያሜ ጥቅምት 1987 ዓ.ም ራሱን ችሎ በአዋጅ ተቋቋመ፡፡
ይህን ስያሜ ይዞ እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ለ20 ዓመታት የመንገድ/ድልድይ ግንባታ እና ጥገና እንዲሁም የኮንትራት አስተዳደር ስራዎችን ሲያከናውን ነበር፡፡ ኤጀንሲዉ በባለስልጣን ደረጃ የተቋቋመበት አዋጅ ቁጥር7/1988 ዓ.ም በ1991፣በ1995 እና በ2005 ዓ.ም ወቅቱ የሚጠይቃቸዉ የአዋጅ ማሻሻያዎች ተካተዉበት አዋጁ እንደገና ተሻሽሎ በመፅደቅ ሲሰራበት የቆየ ሲሆን ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ከኮንትራት አስተዳደር ስራዎች ወጥቶ ‹‹የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ›› በሚል ስያሜ የመንገድ እና ድልድይ ግንባታና ጥገና ስራዎችን የሚያከናውን ተቋም ሆኖ በመደራጀት ተግባርና ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል፡፡
ኤጀንሲው በቀጣይ ከሚመለከታቸዉ አጋር አካላት ጋር ተባብሮ በመስራት የክልሉን ህብረተሰብ የመንገድ ተደራሽነት ጥያቄ ለመመለስ እና በክልሉ በመንገድ እና ድልድይ ግንባታና ጥገና ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ ተቋም ለመሆን አልሞ እየሰራ ይገኛል፡፡