የጎጃም
የጎጃም ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ባለፉት 5 ወራት ከ300 ኪሜ በላይ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ሥራ አከናወነ፡፡
በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የጎጃም ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት እስከ ህዳር መጨረሻ 2018 ዓ.ም ድረስ 295.21 ኪሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ለማከናወን አቅዶ በመደበኛ እና ወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች 359.41 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና በማከናወን የ5 ወሩን ዕቅድ 121.75 % ፣የዓመቱን ዕቅድ ደግሞ 29.6% ማከናወን ችሏል፡፡ባለፉት 5 ወራት ከተከናወነዉ የጥገና ሥራ መካከል 308.41 ኪ.ሜ የሚሆነዉ በመሣሪያ እና በሰዉ ኃይል የጥገና ሥልት የተከናወነ መደበኛ ጥገና ሲሆን ቀሪዉ 51 ኪ.ሜ የሚሆነዉ ደግሞ ወቅታዊ ጥገና ነዉ፡፡
ጥገና ጽ/ቤቱ በአሁኑ ወቅት 102.43 ኪ.ሜ ርዝመት ባላቸዉ ከአጉለሽ- ቡሸት-ገደብ፣ከሰዴ-ከርነዋሪ፣ከአዲስቅዳም- ችጓሌ፣ከችጓሌ- ጥርጊ፣ከባካፍታ - መሰላ፣ከመሰላ - ዋይከላ እና አዲስቅዳም-ፋግታ 7/ሰባት/ የጥገና መስመሮች በመደበኛ እና በወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች ጥገና እያከናወነ ሲሆን የጥገና ሥራዉን በወቅቱ ለማጠናቀቅ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የጎጃም ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በምስራቅ ጎጃም፣ ምዕራብ ጎጃም እና አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞኖች በሚገኙ ነባር የገጠር መንገዶች የጥገና ስራ የሚያከናዉን ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት በ68 የጥገና መስመሮች 1,213.22 ኪሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና በማከናዉን ህብረተሰቡ ተገቢዉን የመንገድ ትራንሰፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ እየሰራ ይገኛል፡፡




የሰሜን ሸዋ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ባለፉት 5 ወራት 212.04 ኪሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ሥራ አከናወነ፡፡
የሰሜን ሸዋ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ስር ከሚገኙ 6/ስድስት/ የገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤቶች መካከል አንዱነዉ፡፡ ጥገና ጽ/ቤቱ በተያዘዉ በጀት ዓመት በ48 የጥገና መስመሮች 845.8 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ለማከናወን አቅዶ እየሰራ ሲሆን እስከ ህዳር መጨረሻ2018 ዓ.ም ባለዉ ጊዜ 212.04 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና በማከናወን የ5 ወሩን ዕቅድ 112.78 % ፣የዓመቱን ዕቅድ ደግሞ 25.1% ማከናወን ችሏል፡፡
የሰሜን ሸዋ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በአሁኑ ወቅት 91.52 ኪ.ሜ ርዝመት ባላቸዉ ከገርባ-ሀርዋ-ሰንቀሌ፣ከኮከብ መስክ-ወረንጨፊ-በሬሳ፣ከሸዋሮቢት-ቀወት እና ከቦሎ-በጣሶ-ንፋስ አምባ-ጅሁር 4/አራት/ የጥገና መስመሮች በመደበኛ እና በወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች ጥገና እያከናወነ ሲሆን የጥገና ሥራዉን በተያዘዉ ዕቅድ መሰረት ለማጠናቀቅ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡የጥገና ሥራ እየተከናወነ ካለባቸዉ አራት የጥገና መስመሮች መካከል 19.92 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ የቦሎ-በጣሶ-ንፋስ አምባ-ጅሁር የጥገና መስመር በተደራጁ ወጣቶች አማካኝነት በሰዉ ኃይል የጥገና ስልት እተከናወነ ያለ ጥገና ነዉ፡፡
የሰሜንቤት ነዉ፡፡ ሸዋ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በሰሜን ሸዋ እና ኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን የሚገኙ የገጠር መንገዶችን በመጠገን ህብረተሰቡ ያልተቋረጠ የመንገድ ትራንሰፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ እየሰራ ያለ ጥገና ጽ/ቤት ነው


ልዩ ልዩ ዜናዎች
የጎጃም ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ባለፉት 5 ወራት ከ300 ኪሜ በላይ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ሥራ አከናወነ፡፡
2018 የተለያዩ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎች ኪራይ አገልግሎት ግዥ (ድጋሚ የወጣ ግልፅ ማስታወቂያ)
ባሕር ዳር: መስከረም 12/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸሙን ገምግሟል።
የአማራ ገጠር መንገደች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋናው መ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች በኤጀንሲው የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ።
የሰሜን ሸዋ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ባለፉት 5 ወራት 212.04 ኪሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ሥራ አከናወነ፡፡
የሰሜን ሸዋ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ስር ከሚገኙ 6/ስድስት/ የገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤቶች መካከል አንዱነዉ፡፡ ጥገና ጽ/ቤቱ በተያዘዉ በጀት ዓመት በ48 የጥገና መስመሮች 845.8 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ለማከናወን አቅዶ እየሰራ ሲሆን እስከ ህዳር መጨረሻ2018 ዓ.ም ባለዉ ጊዜ 212.04 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና በማከናወን የ5 ወሩን ዕቅድ 112.78 % ፣የዓመቱን ዕቅድ ደግሞ 25.1% ማከናወን ችሏል፡፡
የሰሜን ሸዋ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በአሁኑ ወቅት 91.52 ኪ.ሜ ርዝመት ባላቸዉ ከገርባ-ሀርዋ-ሰንቀሌ፣ከኮከብ መስክ-ወረንጨፊ-በሬሳ፣ከሸዋሮቢት-ቀወት እና ከቦሎ-በጣሶ-ንፋስ አምባ-ጅሁር 4/አራት/ የጥገና መስመሮች በመደበኛ እና በወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች ጥገና እያከናወነ ሲሆን የጥገና ሥራዉን በተያዘዉ ዕቅድ መሰረት ለማጠናቀቅ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡የጥገና ሥራ እየተከናወነ ካለባቸዉ አራት የጥገና መስመሮች መካከል 19.92 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ የቦሎ-በጣሶ-ንፋስ አምባ-ጅሁር የጥገና መስመር በተደራጁ ወጣቶች አማካኝነት በሰዉ ኃይል የጥገና ስልት እተከናወነ ያለ ጥገና ነዉ፡፡
የሰሜንቤት ነዉ፡፡ ሸዋ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በሰሜን ሸዋ እና ኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን የሚገኙ የገጠር መንገዶችን በመጠገን ህብረተሰቡ ያልተቋረጠ የመንገድ ትራንሰፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ እየሰራ ያለ ጥገና ጽ/ቤት ነው

