የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የህፃናት ማዋያ ህንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ።

የመንግስት ሠራተኞችን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ ሠራተኞች ሙሉ ትኩረታቸውን በመደበኛ ስራቸው ላይ እንዲያተኮሩ በተለይም በጋብቻ ላይ ያሉ ሴት የመንግስት ሠራተኞች ከወሊድ በኋላ የሚኖርባቸው ድርብርብ ኃላፊነት ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በሌላ በኩል የመንግሰት ሠራተኛው ባለበት የኢኮኖሚ ውስንነት ልጆቹን ለማሳደግ ሞግዚት ለመቅጠር የሚችልበት ሁኔታ አናሳ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡

በመሆኑም በመንግስት መስሪያ ቤቶች አካባቢ የህፃናት ማቆያ ማዘጋጀት ለወላጆችም የአእምሮ እረፍት የሚሰጥ ለህፃናቱ በመንግስት የስራ ስዓት ወላጆቻቸውን በቅርብ እንዲያገኙና በሰለጠነ ሞግዚት እንክባካቤ እንዲያገኙ በማድረግ ትልቅ አስተዋፅዖ አድርጓል፡፡

የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ በመንግስት ተቋማት በውስጥ አቅማቸው የህፃናት ማቆያ በሚያዘጋጁበት ወቅት የሰለጠኑ ሞግዚት መቅጠር እንዲችሉ የስራ መደብ በመፍቀድ በፈጠረው ምቹ ሁኔታ በአብዛኛው የመንግስት ተቋማት የህፃናት ማቆያ እንዲቋቋም በመደረጉ የመንግስት ሠራተኛው ላይ ትልቅ እፎይታ መፍጠር ተችሏል፡፡

በዚህ ምክንያት የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የኤጀንሲው ሠራተኞችን በዚህ ረገድ እየገጠማቸው ያለውን ችግር ለመጋራትና በዘላቂነት ለመፍታት በ388 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ሲያስገነባው የነበረው የህፃናት ማዋያ ህንፃ ግንባታ በመጠናቀቁ በቅርቡ ለአገልግሎት እንደሚውል ይታመናል፡፡

በኤጀንሲው የገነባው የህፃናት ማዋያ ህንፃ መኝታ ቤቶች፣ ሳሎን፣ መመገቢያ ክፍሎች፣ ሽንት ቤቶች፣ የእቃ ማጠቢያ ክፍል፣ የልብስ ማጠቢያ ማሽን ማስቀመጫ፣ ሻወር ቤቶች፣ ቢሮ፣ የህፃናት ጡት ማጥቢያ፣ የመጀመሪያ እርዳታ መስጫ እና ለተንከባካቢ ሞግዚቶች የሚያገለግሉ በአጠቃላይ 18 ክፍሎች አሉት።

በመሆኑም በኤጀንሲው የተገነባው የህፃናት ማዋያ ህንፃ ግንባታው በመጠናቀቁ ለአገልግሎት ሲጀምር እድሚያቸው ከ6 ወር እስከ 4 አመት ላሉ 40 ህፃናት በማዋያነት የሚያገለግል ሲሆን የግንባታ ስራውን በመጠናቀቁ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

ይህ እጅግ ያማረና ደረጃውን የጠበቀ የህፃናት ማዋያ ህንፃ ግንባታ ኤጀንሲው ከፍተኛ በጀት በመመደብ ለሠራተኞች ልጆች አገልግሎት እንዲውል ለማድረግ በኤጀንሲው ከፍተኛ አመራሮች የተወሰደው አርአያነት ያለው ተግባር ያለን ምስጋና ታላቅ ነው፡፡

የመንገድ መሠረተ ልማት ግንባታችን ወጪ ቆጣቢ፣ ጥራት ያለውና ረጅም ግልጋሎት እንዲሰጥ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡

የመንገድ ልማት ሥራ በኪሎ ሜትር ብዛት ብቻ የሚለካ ሳይሆን በጥራቱ፣ በዘላቂነቱ እና ለህብረተሰቡ በሚያመጣው አገልግሎት የሚመዘን ነው።

ጥራት ያለው መንገድ የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል፣ የተሸከርካሪና የመለዋወጫ ወጪን ይቀንሳል፣ የትራንስፖርት ደህንነትን ያረጋግጣል፣ እንዲሁም የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ያጠናክራል።

የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በክልሉ የሚገነቡና የሚጠገኑ መንገዶች እና ድልድዮች የተፈለገውን የጥራት ደረጃ እንዲያሟሉ በመድረግ እየሰራ ይገኛል።

በተለይም አስቸጋሪ የተራራማ መሬት አቀማመጥን በኢንጂነሪንግ ጥበብ በማሸነፍ የሚገነቡ መንገዶች የባለሙያዎችን ክህሎት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የልማት ቁርጠኝነት ያንጸባርቃሉ።

በክልሉ በተራራማና ፈታኝ የቶፖግራፊ ሁኔታዎች ውስጥ ሳይቀር ተራራዎችን በመቁረጥ፣ ገደሎችን በማለፍ እና የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የመንገድ እየተገነባ ይገኛል።

በዚህም ኤጀንሲው የተፈጥሮ እንቅፋቶችን ወደ ልማት እድሎች በመቀየር ህብረተሰቡን ከገበያ፣ ከትምህርት፣ ከጤና እና ከሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶች ጋር በማስተሳሰር ለክልሉ ዘላቂ እድገት መሰረት ለመጣል በከፍተኛ ትጋት በመስራት ላይ ነው።

ኤጀንሲው በየዓመቱ በስድስቱ የጥገና ጽ/ቤቶች በሚከናወኑ የመንገድና የድልድይ ፕሮጀክቶች ላይ የጥራት ቁጥጥርና ክትትል ስራዎችን በስፋት ያከናውናል።

በተጨማሪም በፕሮጀክቶች፣ በኳሪ ሳይቶች እና በግንባታ ግብዓቶች ላይ የጥራት ምርመራና ክትትል በማካሄድ የግንባታ ሥራዎች በተቀመጠው መስፈርት መሰረት እንዲከናወኑ ያደርጋል።

የመንገድ ሀብት አስተዳደርን ለማዘመን የተጠናቀቁ መንገዶችን እና ድልድዮችን በዲጂታል ስርዓት በመመዝገብ ወደ ዳታቤዝ ያስገባል። ይህም የመንገድ ሀብት መረጃዎችን በተደራጀ መልኩ ለማስተዳደርና ለውሳኔ አሰጣጥ ለመጠቀም አስፈላጊ መሰረት ይፈጥራል።

በተጨማሪም የመንገድና የድልድይ ፕሮጀክቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ የመንገድ መስመሮች መረጃ ማጥራት፣ የመንገድ ሁኔታ ጥናት፣ የድልድዮችና የሌሎች ስትራክቸሮች መረጃ መሰብሰብና ማደራጀት በዘመናዊ አሰራር ያከናውናል።

ኤጀንሲው ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በቅልጥፍና እና በተጠያቂነት በማስፈጸም የሚገነቡት መንዶችና ድልድዮች ለረጅም ዘመናት አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ አኳያ የግብዓትና የግንባታ ቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ለክልሉ ዘላቂ ልማት መሰረት የሆነ የመንገድ መረብ ለመገንባት ቁርጠኛ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ሲገልጽ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ነው።                                                      

ወጭ ቆጣቢ፣ ጥራትና ረጅም አገልግሎት የመንገድ ግንባታ ስራዎቻችን መለያዎች ናቸው፡፡

   

የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት የጠቅላላ ርዝመቱ 57%(ፐርሰንት) የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፤ በበጀት ዓመቱ የተለያዬ መጠን ያላቸዉ ስትራክቸሮች ግንባታም እየተከናወነ ነዉ፡፡

የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በተያዘዉ በጀት ዓመት ለአነስተኛ፣መካከለኛ እና ትላልቅ ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም ለቱቦ ቀበራ ሥራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት የስትራክቸር ግንባታ ከሚከናወንባቸዉ ፕሮጀቶች መካከል በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ የሚገኘዉ እና 52 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት አንዱ ነዉ፡፡

የመካነብርሃን -ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በ2012 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ በተከናወነዉ ግንባታ የጠቅላላ ርዝመቱ 57.8% የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፡፡ፕሮጀክቱ በተያዘዉ በጀት ዓመት ከክልሉ መንግስት በተመደበ ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት ከ4 እስከ 15 ሜትር ርዝመት ያላቸዉ 3/ሦሥት/ አነስተኛ እና መካከለኛ ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም የቱቦ ቀበራ ሥራዎችን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ ሲሆን እስከ መጋቢት አጋማሽ 2018 ዓ.ም ድረስ በተከናወነዉ የግንባታ ሥራ የአንድ አነስተኛ ድልድይ ግንባታ ተጠናቋል፡፡ የ2 /ሁለት/ አነስተኛ እና መካከለኛ ድልድዮች ግንባታ ደግሞ የግንባታቸዉ 65% እና 20% ተከናዉኗል፡፡በ4/አራት/ ቦታዎች የሚከናወን የቱቦ ቀበራ ሥራም ተጠናቋል፡፡

የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በክልሉ በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ የሚገኙ እና በመንገድ ያልተገናኙ 7/ሰባት/ ቀበሌዎችን ርዕስ በርስ እና ከዋና መንገድ ጋር በማገናኘት የአካባቢዉን ህብረተሰብ የሚያጋጥሙ ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና አስተዳደራዊ ችግሮች እንዲፈቱ በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡

 

የመንገድ መሠረተ ልማት ግንባታችን ወጪ ቆጣቢ፣ ጥራት ያለውና ረጅም ግልጋሎት እንዲሰጥ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡

የመንገድ ልማት ሥራ በኪሎ ሜትር ብዛት ብቻ የሚለካ ሳይሆን በጥራቱ፣ በዘላቂነቱ እና ለህብረተሰቡ በሚያመጣው አገልግሎት የሚመዘን ነው።

ጥራት ያለው መንገድ የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል፣ የተሸከርካሪና የመለዋወጫ ወጪን ይቀንሳል፣ የትራንስፖርት ደህንነትን ያረጋግጣል፣ እንዲሁም የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ያጠናክራል።

የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በክልሉ የሚገነቡና የሚጠገኑ መንገዶች እና ድልድዮች የተፈለገውን የጥራት ደረጃ እንዲያሟሉ በመድረግ እየሰራ ይገኛል።

በተለይም አስቸጋሪ የተራራማ መሬት አቀማመጥን በኢንጂነሪንግ ጥበብ በማሸነፍ የሚገነቡ መንገዶች የባለሙያዎችን ክህሎት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የልማት ቁርጠኝነት ያንጸባርቃሉ።

በክልሉ በተራራማና ፈታኝ የቶፖግራፊ ሁኔታዎች ውስጥ ሳይቀር ተራራዎችን በመቁረጥ፣ ገደሎችን በማለፍ እና የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የመንገድ እየተገነባ ይገኛል።

በዚህም ኤጀንሲው የተፈጥሮ እንቅፋቶችን ወደ ልማት እድሎች በመቀየር ህብረተሰቡን ከገበያ፣ ከትምህርት፣ ከጤና እና ከሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶች ጋር በማስተሳሰር ለክልሉ ዘላቂ እድገት መሰረት ለመጣል በከፍተኛ ትጋት በመስራት ላይ ነው።

ኤጀንሲው በየዓመቱ በስድስቱ የጥገና ጽ/ቤቶች በሚከናወኑ የመንገድና የድልድይ ፕሮጀክቶች ላይ የጥራት ቁጥጥርና ክትትል ስራዎችን በስፋት ያከናውናል።

በተጨማሪም በፕሮጀክቶች፣ በኳሪ ሳይቶች እና በግንባታ ግብዓቶች ላይ የጥራት ምርመራና ክትትል በማካሄድ የግንባታ ሥራዎች በተቀመጠው መስፈርት መሰረት እንዲከናወኑ ያደርጋል።

የመንገድ ሀብት አስተዳደርን ለማዘመን የተጠናቀቁ መንገዶችን እና ድልድዮችን በዲጂታል ስርዓት በመመዝገብ ወደ ዳታቤዝ ያስገባል። ይህም የመንገድ ሀብት መረጃዎችን በተደራጀ መልኩ ለማስተዳደርና ለውሳኔ አሰጣጥ ለመጠቀም አስፈላጊ መሰረት ይፈጥራል።

በተጨማሪም የመንገድና የድልድይ ፕሮጀክቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ የመንገድ መስመሮች መረጃ ማጥራት፣ የመንገድ ሁኔታ ጥናት፣ የድልድዮችና የሌሎች ስትራክቸሮች መረጃ መሰብሰብና ማደራጀት በዘመናዊ አሰራር ያከናውናል።

ኤጀንሲው ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በቅልጥፍና እና በተጠያቂነት በማስፈጸም የሚገነቡት መንዶችና ድልድዮች ለረጅም ዘመናት አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ አኳያ የግብዓትና የግንባታ ቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ለክልሉ ዘላቂ ልማት መሰረት የሆነ የመንገድ መረብ ለመገንባት ቁርጠኛ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ሲገልጽ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ነው።                                                      

ወጭ ቆጣቢ፣ ጥራትና ረጅም አገልግሎት የመንገድ ግንባታ ስራዎቻችን መለያዎች ናቸው፡፡

   

የወሎ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በዕቅድ የተያዙ የጥገና መስመሮች ሙሉ በሙሉ በመጠገን መንገዶቹ ለህብረተሰቡ ተገቢዉን አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እየሰራ ነዉ፡፡

በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የወሎ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በደቡብ ወሎ ዞን የሚገኙ ነባር የገጠር መንገዶች ተገቢዉን ጥገና እንዲያገኙ በማድረግ ህብረተሰቡ ያልተቋረጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ እየሰራ ያለ ጥገና ጽ/ቤት ነዉ፡፡

ጥገና ጽ/ቤቱ በተያዘዉ በጀት ዓመት በ38 የጥገና መስመሮች በመደበኛ እና ወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች 953 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ለማከናወን አቅዶ እስከ ታህሳሥ 15/2018 ዓ.ም ባለዉ ጊዜ በ23 የጥገና መስመሮች 519.18 ኪ.ሜ መንገድ በመጠገን እስከ ታህሳስ አጋማሽ የተያዘዉን ዕቅድ 129.8%፣የዓመቱን ዕቅድ ደግሞ 54.5% መፈፀም ችሏል፡፡ከተከናወነዉ የጥገና ሥራ መካከል 464.27 ኪ.ሜ(89.4%) የሚሆነዉ መደበኛ ጥገና ሲሆን ቀሪዉ 54.91 ኪ.ሜ(10.6%) የሚሆነዉ ደግሞ ወቅታዊ ጥገና ነዉ፡፡

ጥገና ጽ/ቤቱ በአሁኑ ወቅት 103.2 ኪ.ሜ ርዝመት ባላቸዉ ከደጋን -አዳሜ፣በለጩማ-ዴንሳ፣ወይናምባ-ልጓማ እና ከመሳለሚያ-ሾላዉ 4/አራት/ የጥገና መስመሮች በመደበኛ እና ወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች የጥገና ሥራ እያከናወነ ሲሆን የጥገና ሥራዉን በጥር ወር ዉስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነዉ፡፡

የወሎ ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በበጀት ዓመቱ በዕቅድ የተያዙ ሁሉም የጥገና መስመሮች የጥገና ሽፋን እንዲያገኙ በማድረግ የዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡