ልዩ ልዩ ዜናዎች
2018 የተለያዩ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎች ኪራይ አገልግሎት ግዥ (ድጋሚ የወጣ ግልፅ ማስታወቂያ)
ባሕር ዳር: መስከረም 12/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸሙን ገምግሟል።
የአማራ ገጠር መንገደች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋናው መ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች በኤጀንሲው የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ።
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ አመራሮች እና ሰራተኞች በየዓመቱ የሚከበረዉን የፀረ- ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዉይይት አካሄዱ፡፡
የኤጀንሲዉ ዋና መ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች ‹‹ትዉልድን በሥነ-ምግባር፤ተቋምን በአሠራር›› በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረዉን የፀረ- ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዉይይት በ29/03/2018 ዓ.ም አካሂደዋል፡፡
በዉይይቱ የተቋምን አሠራር ማዘመን ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል ትልቅ ፋይዳ ያለዉ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ለዚህም በተቋማት የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሠራርን የማጠናከር ተግባር በትኩረት መሰራት ያለበት መሆኑ ተመልክቷል፡፡
አሠራርን ከማዘመን ባሻገር አመራሩ እና ሰራተኛዉ ሙያዊ ሥነ-ምግባርን ተላብሶ ተግባራትን ማከናወን ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል የማይተካ ሚና ያለዉ በመሆኑ የአመራሩ እና ሰራተኛዉን ሙያዊ ሥነ-ምግባር ለማጎልበት የሚያስችሉ ተከታታይ ተግባራት መከናወን እንዳለባቸዉም በዉይይቱ ተገልፆል፡፡



